Wednesday, May 29, 2013

ግብረ ሰላም

    
ግብረ ሰላም ማለት ‹‹ ገብረ ሰላመ››መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ሰላምን አደረገ ፤ተጣልተው የነበሩ ሰማያውያን መላዕክት እና ምድራዊያን ደቂቀ አዳም በመስቀሉ ታረቁ ፤ሰላም ወረደ ማለት ነው፡፡ ይሄውም ‹‹የእግዚአብሔር ሙላቱ በእርሱ እንዲኖር በእርሱ በኩልበመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ያሉት ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዷልና› በማለት ቅዱስ ጳውሎስ በቆላ 1፤19-20 ፍንትው አድርጎ ክርስቶስ በመስቀሉ ሰላም እንዳደረገ ገልጾት እናገኛለን፡፡ተድያ ካህናት አባቶች ይህንን ብስራትእና የምስራች ይዘው ከቤተ- እግዚአብሔር ወደ ምዕመናን ቤት‹‹ አዋጅ አዋጅ›› በማለት ይሄዳሉ፡፡ትንሳኤውንም ያበስራሉ፡፡ ይህም ምሰጢር አለው ፡፡ጌታችን እና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቅሎ፤ሞቶ፤ወደ መቃብር በወረደብት ጊዜ ሐዋርያት ፍሩኀን ፤ድንጉጻን ነበሩ፡፡በኋላም በ3ኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ በመነሳት ትንሳኤውን በአበሰራቸው ጊዜ ሐሴት አድርገዋል(ዮሐ 20፤20)፡፡በዚህ መሰረት ካህናት የክርስቶስን ትንሳኤ ይዘው ለሐዋርያት  ምሳሌ ለሆኑት ለምዕመናን ክርስቶስ ተነስቷል እያሉ ብስራቱን ይናገራሉ፡፡ካህናት  ለምዕመናን ‹‹ የክርስቶስ ቸርነቱ ብዛቱ፤40 ፆሙ 50 ብሉ ማለቱ ፤ጾም እንዳትውሉ ፤ዘር እንዳትመትሩ›› በማለት ጊዜው የደስታ፤የሐሴት መሆኑን ይናገራሉ፡፡ምዕመናንም በክርስቶስ ትንሳኤ ደስ በመሰኘት ቀንዱ የዞረዉን፤ጮማው የሰባውን ፤ጠላው የጠራውን አዘጋጅተው ካህናትን፤የቤተ-ክርስቲያን አገልጋዮችን በየቤታቸው በመጥራት የትንሳኤውን በረከት በአንድ ላይ ያከብራሉ፡፡ይህም ግብረ ሰላም ይባላል፡፡  
በሌላ በኩል ግብረ ሰላም ማለት ምዕመናን የክርስቶስን ተዝካር አወጣን በማለት ስለ ግርፋቱ፤ስለ መንገላታቱ፤ስለመሰቀሉ እና ስለመሞቱ በማሰብ እና በማዘን የክርስቶስ ምሳሌ የሆኑትን ካህናን በመጥራት ያከብሩታል፡፡በአንጻሩ ካህናት ምዕመናንን አይዟችሁ ክርስቶስ ምንም መከራ ሞት ቢቀበል ሞቶ አልቀረም ከሙታን ተለይቶ ተነስቷል፡፡ በማለት ደስታን ያበስሯቸዋል፤ትንሳኤውን ይሰብኩለቸዋል፤ያረጋጓቸዋል‹‹ሰላም ….እምይእዜሰ፤ይኩን …ፍስሐ ወሰላም ››በማለት ሰላም መታወጁን ይናገራሉ፡፡
     በግብረ ሰላም ጥሪ አድሎ መኖር የለበትም ፡፡አልያ ግብረ ሰላም መሆኑ ይቀራል፡፡ስለዚህ ግብረ ሰላም ለማድረግ አስቀድሞ

Thursday, May 23, 2013

ፈተና በክርስትና ጉዞ (ክፍል ሁለት)

ምንጭ፦ አትሮንስ - የዲያቆን ኤርምያስ ነቢዩ ገጽ (http://www.ermiasnebiyu.org/)

አንድ ክርስቲያን፤ ክርስቲያን በመሆኑ ብቻ በተለያየ  መልኩ ሊፈተን ይችላል።  ለምሳሌ የግብጽን ክርስቲያኖች ብንመለከት፤ 85% የሚሆነውግብጻዊ እስልምናን ይመርጣል፣የግብጽ መተዳደሪያ የእስላምሻርያ ሕግ እንዲሆን ይፈልጋል፣ የሚሰርቅ ሰው እጆቹ እንዲቆረጡበት ይመኛል፣ ሴቶች እናክርስቲያኖች እንደሁለተኛ ዜጎች ሆነው እንዲኖሩ ያቅዳል። ይህንንም የግብጻውያንን የልብ ትርታበደንብ የተረዱት የእስላም ፓርቲዎች ሴቶች እና ክርስቲያኖች ፕሬዚደንት መሆን እንደማይገባቸው፡እንዲያውም ቁልፍ የሆኑ የሥልጣን ቦታዎችን መያዝ እንደሌለባቸው በመተዳደሪያዎቻቸውአስቀምጠዋል። አሁንም ቢሆን፡ ክርስቲያን ግብጻውያን፡ ፖሊስ መሆን፣ በውትድ ማገልገል፣የእስላም ትምህርት ተቋሞች ውስጥ ገብቶ መማር ወይም ማንኛውም የብሔራዊ የስፖርት ቡድንውስጥ የመሳተፍ መብት የላቸውም። ይህን አሳፋሪ ሁኔታ የዓለም ማሕበረሰብ እንደማያውቅ ሆኖዝም ብሎታል፣ እግዚአብሔር ግን ከቶ አይረሳውም፤ አልረሳቸውምም።
እግዚአብሔርም ለሚወዱት እንደ ሃሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ 8፤28።  ሁልጊዜ እግዚአብሔርን ያለ ማቋረጥ በትእግስት ልንጠብቀው ይገባል። የጻድቁ የዮሴፍን ታሪክ ብንመለከት ወንድሞቹ በቅንአት መንፈስ ተነሳስተው

Monday, May 20, 2013

ቅዱስ ያሬድ ማን ነዉ?


ኢትየጵያዊዉ ቅዱስ ያሬድ ሚያዝያ 5 ቀን 505 ዓ/ም በአክሱም ከተማ ተወለደ፡፡እናቱ ታዉክሊያ/ክርስቲና/አባቱ ደግሞ ይስሐቅ/አብድዩ/ይባላሉ፡፡አባቱ የ አክሱም ጽዮን ቄሰ ገበዝ ነበር፡፡ያሬድ ሰባት ዓመት ሲሆነዉ አባቱ ስለሞቱበት እናቱ ት/ቤት ለማስገባት ወደ አጎቱ መምህር ጌዲዮን ጋር ወሰደችዉ፡፡አባ ጌድዮንም በአክሱም ቤተ ቀጢን(ቤተ ጉባኤ)መምህር ነበሩ፡፡ያሬድ ያኔ በትምህርቱ የሚያሳየዉ ዉጤት ደካማ ስለነበር ከሌሎች ህጻናት ጋር ሊወዳደር አልቻለም፡፡መምህሩ ጌዴዎን ለተግሣጽ ቢቀጡትም መታገስ ተስኖት ተስፋ ቆርጦ ከአክሱም ከተማ ወጥቶ ወደ እናቱ መንደር መደባይ ወለል ተጓዘ፡፡
ህጻን ያሬድ ከዛፍ ስር ተቀምጦ በምን ምክንያት ገጓደኞቹ በታች እንደሆነ ሲያዝን ሲተክዝ ቆየ፡፡ታደሰ አለማየሁ‹‹የቤተ ክርስቲያን ብርሀን ቅዱስ ያሬድ››በሚለዉ መጽሐፉ‹‹አንድ ትል የዛፉን ፍሬ ለመመገብ ፈልጎ ወደላይ እየወጣና እየወደቀ ተደጋጋሚ ሙከራ ሲያደርግ ከቆየ በኋላ በሰባተኛዉ ጊዜ ወጥቶ ፍሬዋን ሲመገብ ተመለከተ፡፡ያሬድም የዚህ ትል ተስፋ አለመቁረጥ ትዕግስቱን ጽናቱን ተመልክቶ‹እኔም ተስፋ ሳልቆርጥ ብዙ ጥረት ካደረኩ እንደዚህ ሊሳካልኝ ይችላል›ብሎ ወደ መምህሩ ለመመለስ ወሰነ ይላል››ያሬድ የ አጎቱ ምክርና ተግሣጽ ለሕይወቱ የሚጠቅም መሆኑን በመረዳቱ ትምህርቱን በትጋት ቢማርና ቢያጠና ያሰበዉ ደረጃ ለመድረስ እንደሚችል በመገንዘብ ወደ መምህሩ ጌዲዮን ጉባኤ ቤት ተመለሰ፡፡መምህሩም ተቀብለዉ አስተማሩት፡፡በአጭር ጊዜ አልገባ ያለዉ ትምህርት ተገልጾለት ትምህርቱን በሚገባ አጠናቀቀ፡፡በኋላም የብሉይና የሐዲስ መምህር ሆኖ በመምህሩ በጌዲዮን ወንበር ተተካ፡፡
የቅዱስ ያሬድ ዜማ እና ዓይነቶቹ
የቅዱስ ያሬድ ዜማ በእግዚአብሔር ፈቃድ የተገለጸለት ለመሆኑ መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡ቅዱስ ያሬድ ዜማዉን ያዘጋጀዉ በሦስት ዓይነት ድምፅ ማለትም በግእዝ፣በዕዝል፣እና በዓራራይ ዜማ ነዉ፡፡እነዚህ የዜማ አይነቶች የአንዱ ድምፅ ከሌላኛዉ ድምፅ ያልተደበላለቀ ወጥ የሆነ ድምፅ አላቸዉ፡፡ዜማዎቹንም በስምንት ምልክቶች ቀምሮታል፡፡የምልክቶች አገልግሎትም በትምህርት ሂደት ጊዜ የጠቋሚነት ሚና በመጫወት ለዜማዉ መጠበቅ አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ናቸዉ፡፡
ቅዱስ ያሬድና አፄ ገብረ መስቀል
ቅዱስ ያሬድ የተነሳዉ ዘጠኙ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ በገቡበት ዘመን ነዉ፡፡በዘጠኙ ቅዱሳን የተተረጎሙት ቅዱሳን መጻሕፍት

እንኳን አደረሳችሁ!!!


Thursday, May 16, 2013

መካነ-ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ዘጎንደር ማን ናት?



በ1650 ዓ/ም በአፄ ፋሲል የታነፀችዉ
መካነ-ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ዘጎንደር ማን ናት?

መካነ ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ቤ/ክ የምsትገኘዉ በጥንታዊቷ መዲና:የነገስታት መናገሻ ፤የሊቃውንት መፍለቂያ እና የባህል ጎተራ በሆነችዉ ጎንደር በአፄ ፋሲል ቤተ መንግስት ቅጽር ዉስጥ ነዉ፡፡ምንም አንኳን አሁን በአጥር ብትከለልም ደብሯ በአፄ ፋሲል በጎንደር ከተተከሉት ከሰባቱ ቀደምት አብያተ ክርስቲያናት ማለትም
v  ከፊት አቦ፣ፊት ሚካኤል፣
v  አደባባይ ኢየሱስ፣
v  እልፍኝ ጊዮርጊስ፣
v  መ/መ/መድኃኔዓለም፣
v  አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል አንዷ ናት፡፡
 መካነ ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ብለዉ የሰየሟትም አፄ ፋሲል  እንደሆኑ ታሪክ ያስረዳል፡፡ግምጃ ቤት የሚለዉን ስም ልታገኝ የቻለችዉም ንጉሱ ቤተ ክርስቲያነኗን ከማፃነሳቸዉ በፊት አሁን ቤተ ክርስቲያኗ ባለችበት ቦታ ወንበር በር በሚባለዉ በኩል በእንቁላል ግንብ ወደዋናዉ ቤተ መንግስት በሚወስደዉ የንጉሱ የዕቃ ግምጃ ቤት ነበር፡፡በዚህም ሳቢያ ይኼንን ስም ልታገኝ ችላለች፡፡
ቤተ ክርስቲያኗ በአፄ ፋሲል ጊዜ የሚያገለግሏት 5-ልዑካን የሚባሉት ሲሆኑ በአፄ ኢያሱ ጊዜ ግን እንደማንኛዉም ደብር የሚያገለግሏት ለቤተ መቅደሱ ቄስ፣ዲያቆን፣ ገበዝ፣ ለቅኔ ማኅሌቱ ደግሞ አለቃ፣ መርጌታ፣ቀኝ ጌታ፣ ግራ ጌታ ፣ከመኳንንቱና ወይዛዝርቱ ጋር በአጠቃላይ 199 አገልጋዮች ተወስኖ ተሰጥቷትም ነበር፡፡
   ይኸች ጥናታዊት ደብር የመጀመሪያዉ አራቱ ጉባኤ የተተከለባት ስትሆን( በነገራችን ላይ አራቱ ጉባኤ ስንል መጽሐፈ ሊቃዉንት፣መጽሐፈ መነኮሳት፣መጽሐፈ ብሉያት፣መጽሐፈ ሐዲሳት ማለታችን ነዉ፡፡) አራቱ ጉባኤ ትምህርት በተለያዩ አባቶች ሲሰጥ ቆይቶ በአፄ ኃ/ስላሴ ዘመነ መንግስት አፄዉ እራሳቸዉ እንዲህ አይነቱ ትምህርት በአንድ ቦታ ብቻ መሰጠት የለበትም በማለት መጽሐፈ ብሉያት በአብየ እግዚእ ኪዳነ ምህረት፣መጽሐፈ ሐዲሳት በመካነ ነገስትግምጃ ቤት ማርያም፣ መጽሐፈ ሊቃዉንት በመ/መ/መድኃኔዓለም፣ መጽሐፈ መነኮሳት በሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምህረት(በለሳቱ ምኢት)ትምህርቱ እንዲሰጥ አዘዉ ለጉባኤዉ በጀት በጅተዉ  ደልደለዉታል፡፡እናም አሁን እርሳቸዉ በደለደሉት መሰረት በቤተ ክርስቲያኗ ያሉት መምህር መጋቤ ወልደ ሰንበት ባይነሳኝ( ብቸኛዉ የአራቱ ጉባኤ መምህር) ምንም እንኳን በአራቱ ጉባኤ የተካኑ ቢሆኑም በንጉሱ እንደተመደበዉ ከመጽሐፈ ሐዲሳት በተጨማሪም የፍትሐ ነገስት ትምህርት በዚሁ ቦታ እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

ቤተ ክርስቲያኗ በድርቡሽ መቃጠሏና በተአምር ከቃጠሎ የተረፈችዉ ስዕለ አድህኖ
  በአፄ ዮሐንስ ዘመነ መንግስት በ1881ዓ/ም ድርቡሽ/መሀዲስቶች/ወደ ጎንደር ዘልቀዉ በመግባት አብያተ ክርስቲያንንና የታሪክ መዘክሮችን ባቃጠሉ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኗ በዉስጧ ከሚገኙ ንዋያተ ቅድሳት ጋር ተቃጥላለች፡፡ጽላቱን ግን አባቶች አስቀድመዉ ወደ ሌላ ቦታ አሸሽተዉት ነበርና መትረፍ ችሏል፡፡መካነ ነገስት ግምጃ ቤት ማርያም ቤ/ክ በተቃተለች ጊዜ ጻድቁ ዮሐንስ ያሳሏት

Wednesday, May 15, 2013

ፈተና በክርስትና ጉዞ ( ክፍል ፩)

በዲያቆን ኤርምያስ ነቢዩ (አትሮንስ:- http://www.ermiasnebiyu.org/)

በክርስትና ሕይወት ላይ የሚመጡ ፈተናዎች ፈተና የሰው ልጅ የ እምነት መለኪያ; የ እምነት መገለጫ ወይም መታወቂያ ነው:: የክርስቶስ ተከታይ ለመሆን የተጠራ ማንም ሰው በጉዞው ወቅት የሚገጥሙት ፈተናዎች አሉ:: እያንዳንዱ ክርስቲያንም በክርስትና ሕይወት ከብዙ የፈተና ሕይወት ጋር ግብግብ ይገጥማል:: ምንጊዜም ክርስትና ባለበት ፈተና አለ:: ፈተና የሌለበት ክርስትና ሕይወት እድገት አያሳይም:: በመሆኑም ባገኘን የፈተና ወጀብ ውስጥ ለማለፍ በዓለማ ጽናት ለመራመድ የምንችለው በገጠመን መከራ ተስፋ ሳንቆርጥ አብዝተን ወደ ጌታ እግዚአብሔር ስንጸልይ ነው:: ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ እኛም የቀረበብን ፈተና እምነታችን የሚለካበት መሆኑን አውቀን በትዕግስት ስንቀበለውና ነጥረን ስንወጣ ክብር እናገኝበታለን:: " በዚህም እጅግ ደስ ይላችኋል፥ ነገር ግን በእሳት ምንም ቢፈተን ከሚጠፋው ወርቅ ይልቅ አብልጦ የሚከብር የተፈተነ እምነታችሁ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ፥ ለምስጋናና ለክብር ለውዳሴም ይገኝ ዘንድ አሁን ለጥቂት ጊዜ ቢያስፈልግ በልዩ ልዩ ፈተና አዝናችኋል።እርሱንም ሳታዩት ትወዱታላችሁ፤ አሁንም ምንም ባታዩት በእርሱ

Wednesday, May 8, 2013

የግንቦት ልደታ ለማርያም ክብረ በዓል


                                                
የእመቤታችን በዓላት
በቀደመዉ ዘመን በዘመነ ብሉይ ‹‹የቤተ መቅደስ መታደስ በዓል››ይከበር እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል፡፡ይህ በዓል እስከ ጌታችን ዘመንም ይከበር ነበር፡፡(ዮሐ 10-22)በሐዲስ ኪዳን እዉነተኛ የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤተ መቅደስ ለሆነችዉ እመቤታችን በስሟ በ ዓል ሊደረግላት ይገባል‹‹የጻድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል›› እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝ 111-7
በተ አምረ ማርያም ላይ በዝርዝር እንደተቀመጠዉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሠላሳ ሦስት በዓላት አሏት ፡፡ከእነዚህ በ ዓላት ሁሉ አስበልጣ የምትወደዉ በዓለ ልደቷን እንደሆነ በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ከዐረብኛ ወደ ግእዝ በተተረጎመዉ እመቤታችን በተለያዩ ሀገራት ያደረገቻችዉን ገቢረ ተአምራት በኢትዮጵያ ከተፈጸሙት ጋር አካቶ የያዘዉ ተአምረ ማርያም በዝርዝር ያስረዳል፡፡
ልደቷ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ከሌለ ተቀባይነት እንዴት ይኖረዋል
በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተካተቱና ምሉዕነት የሌላቸዉ ታሪኮች በአዋልደ መጻሕፍት እንደሚሟሉ ራሱ መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል ለምሳሌ ስለ ቅዱስ ዳዊት የሚናገረዉ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ‹‹የንጉሡም የዳዊት የፊተኛዉና የኋለኛዉ ነገር በነቢዩ በናታን ታሪክ እንዲሁም በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ላይ ተጽፏል›› 1ኛ ዜና 29-29
የእመቤታችን ታሪክ
የእመቤታችን ወላጆች በአብዛኛዉ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ‹‹ሀና››እና ኢያቄም/ዮአኪን በሚለዉ ስም የሚጠሩ ሲሆን ሀና በቤተልሔም ተወልዳ እንዳደገች ታሪክ ያስረዳል፡፡በናዝሬት ገሊላ ለመሥዋዕት የሚሆኑ በጎች የሚያቀርብ እንዲሁም እረኛ

ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በዓል እንኳን አደረሳችሁ!!!

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የልደት መታሰቢያ በዓል ዋዜማ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ አሜን።
“ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ”
ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ : ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ ። (መኃ 4:8 ) 
+++ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም ፤
በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ

አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም +++ ስብሃት ለኪ ማርያም እሙ ለፀሃየ ጽድቅ ለአብ ሙሽራው ለወልድ ወላዲቱለመንፈስቅዱስ ጽርሃ ቤቱ ተፈስሂ ደስ ይበልሽ እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም በተፀነሰች በ9 ወር ከአምስት ቀን የግንቦት መባቻ ዕለት ግንቦት 1 ተወለደች። 
መዝሙረኛው ሶሎሞን አባቱ ዳዊት በራዕይ ያያትና በነገስታትና በነብያት ስትጠበቅ ለኖረችው ለቅድስት ድንግል ማርያም የተናገረው ትንቢት ነበር :: ይህም ትንቢት ልደቷን የተመለከተ ነው :: የተወለደችው እናቷ በስደት እያለች በሊባኖስ ተራራ ላይ ነውና። 

እመቤታችን የተወለደች እለት አባቷ ኢያቄምና እናቷ ሀና ከመጠን በላይ ተደሰቱ። የተወለደችበት ቦታ ግን በስደት በተራራ ላይ በመሆኑ ሀና በድሎት አልታረሰችም። ዘመድ አዝማድ ሊጠይቅ ሲመጣ ሁሉም የአራስ ጥሪ ያለውን ይዞ ሲያመጣ አንዲት ቅን ልቦና የነበራት ነገር ግን እጅግ ድሀ የሆነች ሴት በቤቷ ያለውን ጥራጥሬ አሟጣ ሰብስባ ቀቅላ ንፍሮ አድርጋ ይዛላት ሄዳ ነበር :: አራስ ጥሪው የችግረኛ ቢሆንም ያላትን በማድረጓ እግዚአብሔር ከሌሎች ይልቅ የርሷን ስጦታ ወዶላታል :: ይህም በወንጌል ታሪኳ የተጻፈላትን የዚያችን ሁለት ሳንቲም ሰጥታ የሄደችውን ድሀ መበለት ታሪክ ያስታውሰናል።

እኛም የእመቤታችንን ልደት ለማስታወስ ቤት ውስጥ በተመቻቸው ቦታ ሳይሆን ውጪ ሆነን ንፍሮ ቀቅለን: ምንጣፍ አንጥፈን እናስታውሰዋለን - በግንቦት ልደታ
ዮም ፍስሃ ሆነ !!!! እነሆ ድንግል ተወለደች ለአዳም ዘር ሁሉ ብርሃን ሆነ ያመናችሁ ሁሉ ኑ በድግል ደስ ይበለን።

ለመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች በሙሉ እንኳን ለዚህ ታላቅ ክብረ በአል ዋዜማ በሰላም አደረሳችሁ። 
ለአባ ሕርያቆስ ፤ለቅዱስ ኤፍሬም ፤ለቅዱስ ያሬድ ፤ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጸች ዕመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን።!!!

Saturday, May 4, 2013

ክርስቶስ ካልተነሳ እምነታችሁ ከንቱ ነው!!!



መልዕክት ዘአቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ት/ቤት፤ጎንደር

‹‹……ክርስቶስ ካልተነሳ  እምነታችሁ ከንቱ ነው፡፡….››1ኛቆሮ15፤14
       አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷል ፡፡ሞት በሰው በኩል ስለመጣ ትንሳኤ ሙታን በሰው በኩል ሁኗል ፡፡1ቆሮ 15፤20 የጎሰቆለውን የሰውን ህይወት ያድሰው ዘንድ ወደ ዓለም የመጣው ተቀደሚ እና ተከታይ የሌለው የእግዚአብሔር አብ የባህርይ ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ የሞትን እንቆቅልሽ በሞቱ ፤ሞተን እንዳንቀር በትንሳኤው አረጋግጦልናል፡፡ትንሳኤ ማለት ተንስኦ ካለው የግዕዝ ግስ የተወረሰ ሲሆን የቃሉ ትርጉም መነሳት ፤አነሳ ማለት ነው፡፡በሌላ አጠራር በዓሉ ፋሲካ ይባላል ፡፡በዘመነ ኦሪት ይከበር የነበረው የፋሲካ በዓል እስራኤል ዘስጋ ከባርነት ቀንበር ወደ ነጻነት የተላለፉበት ከሀዘን ወደ ደስታ የተሸጋገሩበት በዓል ነው፡፡ዘፀ12፤14
      ፋሲካ ማለት መሸጋገር ማለት ነው፡፡ዘፀ12፤14 የተጠቀሰው ታሪክ መልዐከ ሞት የዕብራውያንን ቤት እያለፈ ግብጻውያንን በሞት በመቅጣቱ ይህንን ቀን ስጋዊ ነጻነትን የተጎናጸፍንበት ስልሆነ ፋሲካ ብለው ያከብሩታል፡፡የደሙ ምልክት ያለበትን ቤት እያለፈ ሌሎችን መግደል…… በኋለኛው ዘመን ከልዕል መንበሩ ወርዶ በደሙ የሲኦልን ባህር የአዳምን ዘር በማሻገሩ ከኃጢአት ወደ ጽድቅ ከአሳር ወደ ክብር የተሸጋገርንበት በዓል ነው እና ፋሲካ ተብሏል፡፡(ምድር ፋሲካን ተደርጋለች…በክርስቶስ ደም ስለታጠበች )እንዳለ ቅ/ያሬድ በድጓ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዲያቢሎስ ግርማ በሲኦል ከተማ በእሳት ወላፈን ሲገረፍ የኖረዉን ሰዉ ለማዳን በአይሁድ ጅራፍ ተገረፈ፡፡ታላቅ መከራንም ተቀበለ፡፡ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በቅዳሴው‹‹…የማይታመመውን የእርሱን ህማም እንናገራለን….የማይሞተውን የእርሱን ሞት እንናገራለን….ሁሉን የያዘውን ያዙት…የህያው አምልክን ልጅ አሰሩት….በቁጣ ጎተቱት……በፍቅር ተከተላቸው…..ኃጢአትን ይቅር የሚልውን ሀጥእ አሉት በመኳንንት የሚፍረደውን በእርሱ ላይ ፈረዱበት ….ለሱራፌል ዘውድ የሚያቀዳጃቸውን የሾህ አክሊል አቀዳጁት…ለኪሩቤል የግርማ ፤ልብስ የሚያለብሳቸውን ለመዘበት ቀይ ግምጃ አለበሱት……አዳምን የፈጠሩ እጆች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ….በገነት የተመላለሱ እግሮቹ…..በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ…..በአዳም ፊት የህይወት መንፈስ እፍ ያለ አፍ ከሀሞት ጋር የተቀላቀለ የኮመጠጠ መራራን ጠጣ ……..እንደዚህ ያለ ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው? …..እንደዚህ ያለ ትዕግስት እንደምን ያለ ትዕግስት ነው? ….እንደዚህ ያለ ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው? ….እንደዚህ ያለ ሰውን ማፍቀር እንደምን ያለ ፍቅር  ነው?….ፍቅር የአምላክን ልጅ ከዙፋኑ ሳበው….እስከሞትም አደረሰው……..›› በማለት የእለተ ዓርቡን መከራ ይገልጻል ፡፡ጌታችን ከሞተ በኋላ በአዲስ መቃብር ጨምርው ቀበሩት በሦስተኛው ቀን እንደተናገረው መግነዝ ፍቱልኝ ….መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል ተስፋ አስቆርጦን የነበረውን ሞት ድል ነስቶ ተነሳ፡፡እኛም እንዲህ እንድንል አበቃን፡፡‹‹……ሞት ሆይ መውጊያህ የታል..ሲኦል ሆይ ድል መንሳትህ የታል …..››.1ኛ ቆሮ15፤55 ብለን በህይወት ላይ ቆመን በሞት ላይ እንድንዘብት አደረገን፡፡ከመቃብር በስተጀርባ የክብር ትንሳኤ እንዳለ ነገረን ፡፡ቅዱስ ጳውሎስ እንደመሰከረው የጌታችን ትንሳኤ ለእምነታችን መሠረት ነው፡፡‹‹….ክርስቶስ ካልተነሳ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው…..እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት …›› በማለት የክርስቶስ ትንሳኤ  ለምናምነው የክርስትና እምነት መሠረት መሆኑን አስረድቷል፡፡1ቆሮ 15፤14

በጌታችን መቃብር አጠገብ ልናስተውለው የሚጋብን ነገር አለ፡፡አይሁዳውያን ሙቶ የሚቀር መስሏቸው ታላቅ ድንጋይ በመቃሩ ደጃፍ ላይ አንከባለው ዘግተውበት ነበር፡፡ማቴ27፤60 የጌታን መቃብር ሊያዩ የሄዱ ሴቶች እንዲህ አሉ ‹‹…ድንጋዩን ማን ያንከባልልናል…?.››ማር16፤3
¤  ይህ ድንጋይ ቃየል አቤልን የገደለበት ዘፍ4፤1-8 ባቢሎናውያን በሰናኦር ላይ ያቆሙትና እግዚአብሔርን የፈተኑበት የትዕቢት ድንጋይ ዘፍ11፤1-9 ዲያቢሎስ ለጌታችን ደቦ እንዲያደርገው ያቀረበለት የፈተና ድንጋይ ማቴ4፤3 በአጠቃላይ ይህ ድንጋይ መላውን የዓለምን ዘር ያስጨነቀ ፤ያሰቃየ ፤ያስለቀሰ፤ያስተከዘ ሞት ነበር ፡፡መቃበሩ አጠገብ የደረሱት ቅዱሳት አንስትም ያስጨነቃቸው ይኸው ነበር፡፡ ሞት ይይዘው ዘንድ የማይቻል ኃያላን ነን የሚሉት በኃይሉ የሚመረምር በአባቱም ዘንድ በመላእክቱም ዘንድ ፤በሰውም ዘንድ የተመሰገነ የጌትነቱ ክብር በሰማይና በምድር የመላ ወደ ሰማይ ሲያርግ ደም ግባቱ ደም ግባቱ ሰማያትን ያለበሰው የሞትን እንቆቅልሽ በሞቱ የፈታው መድኃኔዓለም  ክርስቶስ ነው፡፡ዲያቢሎስ ይህንን ከቃየል ጀምሮ አቤልን ያስገደለበት ድንጋይ በጌታችን መቃብር ብቻ ላይ ወስኖት አልቀረም፡፡ በዚሁ ዘመንም ይጠቀምበታል፡፡የበደልናኃጢአት ድንጋይ ፤ተስፋ የሚያስቆርጥ ድንጋይ፤የኑፋቄ ድንጋይ፤በሰው ልጆች ላይ እየጫነው ይገኛል፡፡ነገር ግን ወደ ሞተልን አምላክ ብንቀርብ ይህን ድንጋይ ከላያችን ላይ ያነሳዋል፡፡ማቴ11፤28 በአጠቃላይ
        የክርስቶስ ትንሳኤ ለዕምነታችን መሠረት ነው፡፡1ቆሮ15፤12
        ክብራችን ነው፡፡ሉቃ24፤13
        ሙተን እንዳንቀር የተበሰረበት ነው፡፡ዮሐ11፤25
        ጠላት የተዋረደበት ነው፡፡ቆላ2፤15
        ሲኦል ባዶውን የቀረበት ነው፡፡1ጴጥ3፤18-20
        ሞት የሞተበት ታላቅ በዓል ነው፡፡1ቆሮ15፤55
አምላክ ወልደ አምላክ ሞተ ፤የሰውን ልጅ ከሞት ያደን ዘንድ ሞተ ፤ሞት በሰው በኩል መጥቶ ነበርና ሰው ሁኖ ሞቶ ሞትን ሻረ ፤ለዚህ ነው ሐዋርያው ክርስቶስ ካልተነሳ እምነታችሁ ከንቱ ናት ያለው፡፡በመሆኑም ይህንን ታላቅ በዓል ስናከበር
v  በደዌ ዳኛ ፤በአልጋ ቁራኛ ተይዘው አስታማሚ በማጣት የሚሰቃዩት ህሙማን
v  እናት አባታቸውን በሞት ተነጥቀው አሰዳጊ አልባ የቀሩትና ለጎዳና ተዳዳሪነት የተዳረጉት ህጻናትን
v  ጧሪ ቀባሪ በማጣት ቤታቸው ፈርሶ ለልመና እጅ የሰጡትን አረጋውያን
v  በስር እየማቀቁ ያሉ የህግ ታራሚዎችን
v  ንብረታቸውን በትነው‹‹ ነገ ያልፍልኛል›› በማለት  ከአንዱ ቀየ ወደ ሌላው ቀየ ……ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላው ሀገር የሚባዝኑትን ስደተኞችን በማሰብና ለእነዚህ ወገኖቻችን አቅማች እንደፈቀደ የምንችለውን ሁሉ በማድረግ ሊሆን ይገባል ፡፡
‹‹ በሞቱ ያዳነን …..በስሙ ያከበረን መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር የተመሰገነ ይሁን ››
‹‹የሰላም በዓል ያድርግልን……ወስብሐት ለእግዚአብሔር…….››

Wednesday, May 1, 2013

ብሂለ አበዉ ስለ ነገረ ህማማት


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
                    ብሂለ አበዉ ስለ ነገረ ህማማት
‹‹እጆቹን እግሮቹን በተቸነከረባቸዉ ችንካሮች መወጋቱን እናምናለን ነቢዩ  ኢሳይያስ እርሱ ደዌያችንን ወስዶ ህማማችን ተሸከመ እንዳለ››ቅዱስ ጎርጎርዮስ ሊቀ ጳጳስ
‹‹ነፍሱን ከስጋዉ በለየ ጊዜ በሲኦል ፈጥኖ ብርሃን ታየ ጌታችን በአካለ ስጋ ሳይሆን በ አካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ሄደ ሲኦልም ተናወጠች መሰረቶቿም እፈርስ እፈርስ አሉ››ቅዱስ አትናቴዎስ ዘ እስክንድርያ
‹‹የሚሰዋ በግ እርሱ ነዉ የሚሰዋ ካህን እርሱ ነዉ፡፡ከባሕርይ አባቱ ከ አብ ከባሕርይ ህይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም መስዋዕት የሚቀበል እርሱ ነዉ፡፡››ያዕቆብ ዘ ስሩግ
‹‹ኃጢአታችን ለማሰተሰርይ በስጋ እንደታመመ እንደሞተ ከነፍሱም በተለየ ጊዜ ስጋዉን እንደገነዙ እናምናለን››የ ኢየሩሳሌም ኤጲስ ቆጶስ ቅ/ዮሐንስ
‹‹ምትሐት ያይደለ በእዉነት ተራበ ተጠማ ዳግመኛም ከኃጥአን ጋር በላ ጠጣ››ቅ/ባስልዮስ ዘ ቂሳርያ
‹‹ከ አብ ጋር አንድ እንደመሆንህ ሞት የሌለብህ አንተ ነህ ከእኛም ጋር አንድ እንደመሆንህ በፈቃድህ የሞትክ አንተ ነህ››ቅ/ኤራቅሊስ
                            ይኼን ያዉቁ ኑሯል
በሰሙነ ህማማት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ የተከናወኑት ተግባራት እንመልከት
ሰኞ፡-ጌታችን ከቢታንያ ሲወጣ ተራበ ቅጠል ያለባትን በለስ ከሩቁ አይቶ በለሲቱን ቀረባት ነገር ግን ከቅጠል በቀር ምንም አልተገኘባትም ከአሁን ጀምሮ ማንም ከ አንች ፍሬን አይብላ ብሎ እረገማት በለስ የተባሉ እስራኤላዊያን ናቸዉ፡፡
ማክሰኞ፡-ሻጮች እና ለዋጮችን ከቤተ መቅደስ ባሶጣ ጊዜ ይኼንን በማን ኃይል እንዳደረገዉ የአይሁድ መምህራን ጠይቀዉት ነበር ማቴ 21-23 ስለሆነም የጥያቄ ቀን ይባላል፡፡
ረቡዕ፡-ምክረ አይሁድ ይባላል ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናት እና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸዉ ምክር ያጠናቀቁበት ቀን በመሆኑ
ሐሙስ፡-በቤተ ክርስቲያን የተለያየ ስያሜዎች ያሏቸዉ በርካታ ድርጊቶች የተፈጸሙበት ነዉ፡፡
  ûጸሎተ ሐሙስ ይባላል፡መድኃኒዓለም ክርስቶስ አይሁድ መጥተዉ እስኪይዙት ድረስ ሲጸልይ ያደረበት ነዉና ጸሎተ ሐሙስ ተባለ
ûሕጽበተ ሐሙስ ይባላል፡-ጌታችን በዚህ ዕለት የደቀ መዛሙርቱን እግር ጎንበስ ብሎ በታላቅ ትህትና አጥቧልና
û የሚስጢር ቀን ይባላል፡-ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የሆነዉን ምስጢረ ቁርባን በዚህ ዕለት ተመስርቷልና
û የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል፡-ምክንያቱም የ ኦሪት መስዋዕት የሆነዉ ያእንስሳት ደም ማብቃቱን ገልጦ ለድህነተ ዓለም ራሱን የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ያቀረበበት ዕለት በመሆኑ
û የነፃነት ሐሙስ ይባላል፡-ምክንያቱም ለኃጢአትናለዲያብሎስ ባርያ መሆኑ ማብቃቱና የሰዉ ልጅ ያጣዉን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነ ነዉ፡፡
ዓርብ፡-ጌታችን ከ ጲላጦስ አደባባይ እስከ ሊጦስጥራ የተንገላታበት ለአዳምና ለልጆቹ በምልዕልተ መስቀል ለሞት እራሱን አሳልፎ የሰጠበት ቀን ነዉ፡፡
ቅዳሜ፡-በዚች ዕለት የጌታችን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትዉል ቅዳም ሥዑር ወይም የተሻረችዉ ቅዳሜ ትባላለች፡፡ካህናቱም ለምዕመናን ለምለም ቄጤማን የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ ለምለም ቅዳሜም ትባላለች፡፡እንደዚሁም ልዑል እግዚአብሔር በዚህ ቀን 22ቱን ስነ ፍጥረታት ፈጥሮ ከስራዉ ያረፈበት ዕለት በመሆኑ ቅ/ቅዳሜ ይባላል፡፡
                                  ዳክርስ
       ፀሐይ ብርሃኗ ነጥፎ የበርባኖስ ክንብንብ ስታጠልቅ
      ጨረቃ በሀዘን ተዉጣ በደም አበላ ስትጠመቅ
     ተፈጥሮ ስርዓቷ ተዛብቶ ቀኑ በጽልመት ሲቀየር
      አለታት በፍርሀት ተንጠዉ በድን አካላቸዉን ሲንሞሱ
      ወዳጅህ ልቡ ተነክቶ አንተን  ለድህነት ሲጠራህ
      ህይወት በቀኝህ ተሰቅሎ የቀለጠ ፍቅሩን ስታይ
      በመጨረሻዋ ደቂቃ ህይወትን መዋጀት ሲገባህ
      ታአምሩን በአይኖችህ እያየህ ቃሉን በጀሮህ እየሰማህ
       ምን የሚሉት ፈሊጥ ነዉ ይኼ በበደል ላይ በደል ማከል
       ልብን ተራራ አሳክሎ አንደበትን ለስድብ ማሾል
      ልብህ ባለማመን እረግረግ በክህደት አረንቋ ተጣለ
      ዋ!ምነዋ! ዳክርስ የእምነት ቋጥህ ሟጠጠ
                              ሰባቱ የመስቀል ላይ ንግግሮች
& ኤሎኼ ኤሎኼ ኤልማስ ላማ ሰበቅታኒ ትርጓሜዉም አምላኬ አምላኬ ለምን ተዉኽኝ
& አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያዉቁምና ይቅር በላቸዉ
& አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ
& ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትዉላለህ
&ተጠማሁ
& እነሆ ልጅሽ እነኋት እናትህ
& የተጻፈዉ ሁሉ ተፈጸመ
                          ወስብሐት ለእግዚአብሔር