Tuesday, April 2, 2013

ዕድሜህ ስንት ነዉ?



ስንት ዓመት ኖረሀል?
ምን አሳልፈሀል
ምንስ ቀርቶብሃል?
ዕንደ ያዕቆብ እየዉ
ዞረህ ወደ ኋላ
ስትቀርብ ሚርቅህን
የዕድሜህን ጥላ
ስንት ዓመት አለፈህ
ጌታህን ካወቅኸዉ
ተመችተኸዋል
ወይስ ቆረቆርኸዉ
እንዲያዉ ለማደግህ
ምን ምልክት አለህ
የኃጢአት ጡጦህን
ጣልከዉ ትጠባለህ?
ዛሬም እንደ አምናዉ
ዳዴን አልጨረስክም?
ማደግህ እንዲታወቅ
መራመድ አልቻልክም?
አሊያማ ከደፈርክ
አደኩኝ ለማለት
ስንት ዓመት ኖረሀል
ምንስ ሠራህበት
                       ዘፍ 47-8
             ከወርቅነሽ ቱፋ

No comments:

Post a Comment