Thursday, March 14, 2013

ወይ ትዕግስት?


ድምፁን ሰምቼ እበሬ
ብከፍተው ቆሞ መምህሬ
ፍቅር ተርቦ እራቱን
አየሁት ያዘነ ፊቱን
ገረመኝ የትዕግሥቱ ጫፍ
ያቆመው አመታት ደጃፍ
እንዴት እስካሁን ጠብቆ
አልሄደም ከቤቴ ርቆ?
ተነጥፈው የሚሰግዱለት
ዘጠና ዘጠኝ እያሉት
ምን ይገደዋል መድኅኔ?
ልጅ ላልሆንኩለት ለኔ


መንግስተ ሰማያት ቀርባለች እና ንስሐ ግቡ!!!

No comments:

Post a Comment