Friday, March 15, 2013

ዜና

ዜና አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ት/ቤት

የደብረ ምሕረት አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ትምህርት ቤት በሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳድር ማረሚያ ቤት የተጠናከረ የወንጌል አገልግሎት መስጠት ጀመረ።  በማረሚያ ቤቱ የሚገኙ ክርስቲያን ታራሚዎች ከዚህ ቀደም የተጠናከረ መንፈሳዊ ትምህርት ማግኘት አለመቻላቸውን ጠቅሰው ሰንበት ትምህርት ቤቱ በራሳቸው ተነሳሽነት በቅዱስ መጽሐፍ እንደታዘዘው ወንጌል የተራብነውን እኛን እዚህ ድረስ በመምጣት ማገልገሉን ሊመሰገን ይገባዋል ብለዋል።  ሰንበት ትምህርት ቤቱ በማረሚያ ቤቱ በዕለተ እሁድ ለሁለት ሰዓት የሚቆይ ስብከት፤ ያሬዳዊ ዝማሬ እንዲሁም አጽናኝ የሆኑ ስነ ጽሑፎችን የሚያቀርብ ሲሆን በሳምንት አንድ ቀን በሚያካሂደው በዚህ መንፈሳዊ ዝግጅት ተቋዳሽ የሆኑ የህግ ታራሚዎች ይበል የሚያሰኝ የባሕርይ ለውጥ ማምጣታቸውን ለመረዳት ተችሏል።

No comments:

Post a Comment