Monday, March 18, 2013

የአብይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት (ቅድስት)

ምንጭ፦ የዲያቆን ኤርምያስ ነቢዩ ገጽ (www.ermiasnebiyu.org)


በዚህ በመጀመርያው ሳምንት ከመዝሙረ ዳዊት ላይ የሚሰበከው ምስባክ፦

በግዕዝ፦ 

እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ
አሚን ወሰናይት ቅድሜሁ
ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ

በአማርኛ፦ 

እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ።
ምስጋናና ውበት በፊቱ ነው፥
ቅዱስነትና ግርማ በመቅደሱ ውስጥ ናቸው። (መዝ.፺፭(፺፮)፡፭


በዚህ የሁለተኛ የአብይ ጾም ሳምንት ስለ እግዚአብሔር ቅድስና ቤተ
ክርስቲያን ልጆቿን ታስተምራለች። እግዚአብሔር ቅዱስ በመሆኑ የተቀደሰ ነገርያስፈልገዋልና ሰው ሁሉ በቅድስና መንገድ በመመላለስ የክብሩ ባለቤት የመንግሥቱ ወራሽእንዲሆን እግዚአብሔር እኔ ቅዱሳን ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ በማለት ስለማስተማሩ ሰፊትምህርት ይሰጥበታል። ሰውም፤ መላእክትም፤ ቦታም፤ ዕለትም
ለእግዚአብሔር በእግዚአብሔር ተቀድሰዋል። ቅዱሳን መላእክትና ቅዱሳን ሰዎችየእግዚአብሔርን ቅድስና ተረድተው እግዚአብሔርን በማመስገን ሲተጉ ቅዱሳት ቦታዎችእና ዕለታት የቅዱሳኑ ነገር ሲታሰብባቸው፤ ጸሎት ሲደርስባቸው እና ለእግዚአብሔር እናእግዚአብሔር ለቀደሳቸው ቅዱሳን ስም መጠሪያ ሆነው ሲያገለግሉ ይኖራሉ።እግዚአብሔርን ማየት እና የእግዚአብሔር የሆነን ሥርዓት መከተል ስለሚያስችል ዕለትዕለት መልካም በማድረግ ቤተ መቅደስ ተብሎ የተነገረለትን ሰውነታችንን በመጠበቅለእግዚአብሔር የተቀደሰ ዕቃ ሆነን መቅረብ እንደሚገባ
ይዘከርበታል። እግዚአብሔር አምላካችን ቅዱስ ነው እያልን በልባችን አምነን በአፋችን
መስክረን በተግባር ግን ከቅድስና ርቀን እንዳንኖር እግዚአብሔር እንደቀደሰን እናልጅነትን እንደሰጠን በማመን በተቀደሰ ሁኔታ መኖር ይገባናል። የእግዚአብሔርን ቅድስናእንዲሁም ደግሞ እግዚአብሔር ለሰዎች ቅድስናን እንደሚሰጥ ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍልየተለያዩ ክፍሎች እንዲህ በማለት ይገልጸዋል፦

እግዚአብሔርን በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየሁት፥ የልብሱም ዘርፍ
መቅደሱን ሞልቶት ነበር። ሱራፌልም ከእርሱ በላይ ቆመው ነበር፥ ለእያንዳንዱም
ስድስት ክንፍ ነበረው፤ በሁለት ክንፍ ፊቱን ይሸፍን ነበር፥ በሁለቱም ክንፍ እግሮቹን
ይሸፍን ነበር፥ በሁለቱም ክንፍ ይበር ነበር። አንዱም ለአንዱ። ቅዱስ፥ ቅዱስ፥
ቅዱስ፥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ
ይጮኽ ነበር። የመድረኩም መሠረት ከጭዋኺው ድምፅ የተነሣ ተናወጠ፥ ቤቱንም
ጢስ ሞላበት። ኢሳ.፮፡፩-

በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው። ወደ ዓለም እንደ ላክኸኝ እንዲሁ እኔ
ወደ ዓለም ላክኋቸው፤ እነርሱም ደግሞ በእውነት የተቀደሱ እንዲሆኑ እኔ ራሴን ስለ
እነርሱ እቀድሳለሁ። ዮሐ.፲፯፡፲፯-፲፱

ሁሉን የምትገዛ ጌታ አምላክ ሆይ፥ ሥራህ ታላቅና ድንቅ ነው፤ የአሕዛብ ንጉሥ
ሆይ፥ መንገድህ ጻድቅና እውነተኛ ነው፤ ጌታ ሆይ፥ የማይፈራህና ስምህን
የማያከብር ማን ነውአንተ ብቻ ቅዱስ ነህና፥ የጽድቅም ሥራህ ስለ ተገለጠ
አሕዛብ ሁሉ ይመጣሉ በፊትህም ይሰግዳሉ እያሉ የእግዚአብሔርን ባሪያ የሙሴን
ቅኔና የበጉን ቅኔ ይዘምራሉ። ራእ.፭፡፫-

በዚህ በሁለተኛው ሳምንት በቅዳሴ ላይ የሚነበቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ሙሉውምንባብ
ከዚህ የሚከተሉት ናቸው፦

እንግዲህ በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ልትመላለሱ እግዚአብሔርንም ደስ
ልታሰኙ እንዴት እንደሚገባችሁ ከእኛ ዘንድ እንደ ተቀበላችሁ፥ እናንተ ደግሞ
እንደምትመላለሱ፥ ከፊት ይልቅ ትበዙ ዘንድ በጌታ በኢየሱስ እንለምናችኋለን
እንመክራችሁማለን። በጌታ በኢየሱስ የትኛውን ትእዛዝ እንደ ሰጠናችሁ
ታውቃላችሁና። ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም መቀደሳችሁ ነውና፤
ከዝሙት እንድትርቁ፥ እግዚአብሔርን እንደማያውቁ አሕዛብ በፍትወት ምኞት
አይደለም እንጂ፥ ከእናንተ እያንዳንዱ የራሱን ዕቃ በቅድስናና በክብር ያገኝ
ዘንድ እንዲያውቅ፤ አስቀድመን ደግሞ እንዳልናችሁና እንደ መሰከርንላችሁ፥
ጌታ ስለዚህ ነገር ሁሉ የሚበቀል ነውና ማንም በዚህ ነገር አይተላለፍ
ወንድሙንም አያታልል። ለርኵሰት ሳይሆን እግዚአብሔር በቅድስና ጠርቶናልና።
እንግዲህ የሚጥል ሰውን የጣለ አይደለም፥ መንፈስ ቅዱስን በእናንተ እንዲኖር
የሰጠውን እግዚአብሔርን ነው እንጂ። እናንተ ራሳችሁ እርስ በርሳችሁ
ልትዋደዱ በእግዚአብሔር ተምራችኋልና ስለ ወንድማማች መዋደድ ማንም
ይጽፍላችሁ ዘንድ አያስፈልጋችሁም፤ እንዲሁ በመቄዶንያ ሁሉ ላሉት
ወንድሞች ሁሉ ታደርጋላችሁና። ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ከፊት ይልቅ
ልትበዙ፥ በጸጥታም ትኖሩ ዘንድ ልትቀኑ፥ የራሳችሁንም ጉዳይ ልትጠነቀቁ፥
እንዳዘዝናችሁም፥ በውጭ ባሉት ዘንድ በአገባብ እንድትመላለሱ፥ አንዳችም
እንዳያስፈልጋችሁ በእጃችሁ ልትሠሩ እንለምናችኋለን። ነገር ግን፥ ወንድሞች
ሆይ፥ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ አንቀላፍተው
ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን። ፩ተሰ.፬፡፩-፲፫

ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጥቃችሁና በመጠን ኖራችሁ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ
ሲገለጥ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ። እንደሚታዘዙ ልጆች
ባለማወቃችሁ አስቀድሞ የኖራችሁበትን ምኞት አትከተሉ። ዳሩ ግን። እኔ ቅዱስ
ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ
በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ። ለሰው ፊትም ሳያደላ በእያንዳንዱ ላይ እንደ
ሥራው የሚፈርደውን አባት ብላችሁ ብትጠሩ በእንግድነታችሁ ዘመን በፍርሃት
ኑሩ። ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር
ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር
የክርስቶስ ደም እንደ ተዋጃችሁ ታውቃላችሁ። ዓለም ሳይፈጠር እንኳ
አስቀድሞ ታወቀ፥ ነገር ግን እምነታችሁና ተስፋችሁ በእግዚአብሔር ይሆን
ዘንድ፥ ከሙታን ባስነሣው ክብርንም በሰጠው በእግዚአብሔር በእርሱ
ስለምታምኑ ስለ እናንተ በዘመኑ መጨረሻ ተገለጠ። ለእውነት እየታዘዛችሁ
ግብዝነት ለሌለበት ለወንድማማች መዋደደ ነፍሳችሁን አንጽታችሁ እርስ
በርሳችሁ ከልባችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ። ዳግመኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ
ዘር አይደለም፥ በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ
ዘር ነው እንጂ። ሥጋ ሁሉ እንደ ሣር ክብሩም ሁሉ እንደ ሣር አበባ ነውና፤
ሣሩ ይጠወልጋል አበባውም ይረግፋል፤ የጌታ ቃል ግን ለዘላለም ይኖራል።
በወንጌልም የተሰበከላችሁ ቃል ይህ ነው። ፩ጴጥ.፩፡፲፫-፳፭

የተናገረውም መልአክ በሄደ ጊዜ፥ ከሎሎዎቹ ሁለቱን፥ ከማይለዩትም ጭፍሮቹ
እግዚአብሔርን የሚያመልክ አንዱን ወታደር ጠርቶ፥ ነገሩን ሁሉ ተረከላቸው
ወደ ኢዮጴም ላካቸው። እነርሱም በነገው ሲሄዱ ወደ ከተማም ሲቀርቡ፥
ጴጥሮስ በስድስት ሰዓት ያህል ይጸልይ ዘንድ ወደ ጣራው ወጣ። ተርቦም ሊበላ
ወደደ፤ ሲያዘጋጁለት ሳሉም ተመስጦ መጣበት፤ ሰማይም ተከፍቶ በአራት
ማዕዘን የተያዘ ታላቅ ሸማ የሚመስል ዕቃ ወደ ምድር ሲወርድ አየ፤
በዚያውም አራት እግር ያላቸው ሁሉ አራዊትም በምድርም የሚንቀሳቀሱት
የሰማይ ወፎችም ነበሩበት። ጴጥሮስ ሆይ፥ ተነሣና አርደህ ብላ የሚልም
ድምፅ ወደ እርሱ መጣ። ጴጥሮስ ግን። ጌታ ሆይ፥ አይሆንም፤ አንዳች
ርኵስ የሚያስጸይፍም ከቶ በልቼ አላውቅምና አለ። ደግሞም ሁለተኛ።
እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው የሚል ድምፅ ወደ እርሱ መጣ።
ይህም ሦስት ጊዜ ሆነ፥ ወዲያውም ዕቃው ወደ ሰማይ ተወሰደ። ጴጥሮስም
ስላየው ራእይ። ምን ይሆንብሎ በልቡ ሲያመነታ፥ እነሆ፥ ቆርኔሌዎስ
የላካቸው ሰዎች ስለ ስምዖን ቤት ጠይቀው ወደ ደጁ ቀረቡ፤ ድምፃቸውንም
ከፍ አድርገው። ጴጥሮስ የተባለው ስምዖን በዚህ እንግድነት ተቀምጦአልን?
ብለው ይጠይቁ ነበር። ጴጥሮስም ስለ ራእዩ ሲያወጣ ሲያወርድ ሳለ፥
መንፈስ። እነሆ፥ ሦስት ሰዎች ይፈልጉሃል፤ ተነሥተህ ውረድ፥ እኔም
ልኬአቸዋለሁና ሳትጠራጠር ከእነርሱ ጋር ሂድ አለው። ጴጥሮስም ወደ ሰዎቹ
ወርዶ። እነሆ፥ የምትፈልጉኝ እኔ ነኝ፤ የመጣችሁበትስ ምክንያት ምንድር ነው?
አላቸው። እነርሱም። ጻድቅ ሰው እግዚአብሔርንም የሚፈራ በአይሁድም
ሕዝብ ሁሉ የተመሰከረለት የመቶ አለቃ ቆርኔሌዎስ ወደ ቤቱ ያስመጣህ ዘንድ
ከአንተም ቃልን ይሰማ ዘንድ ከቅዱስ መልአክ ተረዳ አሉት። እርሱም ወደ
ውስጥ ጠርቶ እንድግድነት ተቀበላቸው። በነገውም ተነሥቶ ከእነርሱ ጋር
ወጣ፥ በኢዮጴም ከነበሩት ወንድሞች አንዳንዶቹ ከእርሱ ጋር አብረው ሄዱ።
በነገውም ወደ ቂሣርያ ገቡ፤ ቆርኔሌዎስም ዘመዶቹንና የቅርብ ወዳጆቹን
በአንድነት ጠርቶ ይጠባበቃቸው ነበር። ጴጥሮስም በገባ ጊዜ ቆርኔሌዎስ ተገናኝቶ
ከእግሩ በታች ወደቀና ሰገደለት። ጴጥሮስ ግን። ተነሣ፤ እኔ ራሴ ደግሞ ሰው
ነኝ ብሎ አስነሣው። ከእርሱም ጋር እየተነጋገረ ገባ፥ ብዙዎችም ተከማችተው
አግኝቶ። አይሁዳዊ ሰው ከሌላ ወገን ጋር ይተባበር ወይም ይቃረብ ዘንድ
እንዳልተፈቀደ እናንተ ታውቃላችሁ፤ ለእኔ ግን እግዚአብሔር ማንንም ሰው
ርኵስና የሚያስጸይፍ ነው እንዳልል አሳየኝ፤ ስለዚህም ደግሞ ብትጠሩኝ
ሳልከራከር መጣሁ። አሁንም በምን ምክንያት አስመጣችሁኝብዬ
እጠይቃችኋለሁ አላቸው። ቆርኔሌዎስም እንዲህ አለው። በዚች ሰዓት የዛሬ
አራት ቀን የዘጠኝ ሰዓት ጸሎት በቤቴ እጸልይ ነበር፤ እነሆም፥ የሚያንጸባርቅ
ልብስ የለበሰ ሰው በፊቴ ቆመና። ሐዋ.፲፡፯-

በዚህ በመጀመርያው ሳምንት ከመዝሙረ ዳዊት ላይ የሚሰበከው ምስባክ፦

በግዕዝ፦ 

እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ
አሚን ወሰናይት ቅድሜሁ
ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ

በአማርኛ፦ እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ።
ምስጋናና ውበት በፊቱ ነው፥
ቅዱስነትና ግርማ በመቅደሱ ውስጥ ናቸው። (መዝ.፺፭(፺፮)፡፭

በዚህ በመጀመርያው ሳምንት የሚነበበው የወንጌል ክፍል፦

ስትጦሙም፥ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ፤ ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ
ፊታቸውን ያጠፋሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል። አንተ ግን ስትጦም፥
በስውር ላለው አባትህ እንጂ እንደ ጦመኛ ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም
ታጠብ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል። ብልና ዝገት በሚያጠፉት ሌቦችም
ቆፍረው በሚሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በምድር ላይ መዝገብ አትሰብስቡ፤ ነገር ግን ብልም
ዝገትም በማያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በማይሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ
ሰብስቡ፤ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና። የሰውነት መብራት ዓይን ናት።
ዓይንህ እንግዲህ ጤናማ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፤ ዓይንህ ግን ታማሚ
ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል። እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ፥
ጨለማውስ እንዴት ይበረታለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤ ወይም
አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም ይወዳል፤ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንምይንቃል፤
ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም። ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ስለ ነፍሳችሁ
በምትበሉትና በምትጠጡት፥ ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ ነፍስ
ከመብል ሰውነትም ከልብስ አይበልጥምንማቴ.፮፡፲፮-፳፭

1 comment: