Wednesday, March 27, 2013

መፃጉዕ


አትምኢሜይል
  source:- MAHIBERE KIDUSAN                                                                                                                                                                                                        በእመቤት ፈለገ
ልጆች በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት የዓብይ ጾም አረተኛ እሑድ መጻጉዕ
 ይባላል፡፡ ታሪኩም እንደዚህ ነው፡፡ በኢየሩሳሌም በር አጠገብ ቤተሳይዳ የምትባል የመጠመቂያ ቦታ ነበረች በዚያም
ማየት የተሳናቸው፣ መራመድ የማይችሉ ብዙ በሽተኞች በመጠመቂያው ቦታ ተኝተው የውሃውን መናወጥ ይጠባበቁ ነበር፡፡
 ለምን መሰላችሁ ልጆች የእግዚአብሔር መልአክ ወደ መጠመቂያው ወርዶ ውኃውን በሚያናውጠው ጊዜ÷ ከውኃው መናወጥ
 በኋላ በመጀመሪያ ወርዶ የሚጠመቅ ካለበት ደዌ ሁሉ ይፈወስ /ይድን/ ነበር፡፡ በዚያ ቦታም ከታመመ ሰላሳ ስምንት
ዓመት የሆነው አንድ ሰው ነበር፡፡ ስሙም መጻጉዕ ይባላል፡፡ ልጆች መጻጉዕ እንዴት በሕመም እንደተሰቃየ አያችሁ?


ታዲያ ልጆች ጌታችን ኢየሱስ ያሰው በአልጋው ተኝቶ ባየ ጊዜ በበሽታ ብዙ ዘመን እንደቆየ አውቆ “ልትድን ትወዳለህን?” አለው፡፡
 መጻጉዕም “አዎን ጌታዬ ሆይ ነገር ግን ውኃው በተናወጠ ጊዜ ወደ መጠመቂያው የሚያወርደኝ ሰው የለኝም፤ እኔ በምመጣበት
 ጊዜ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል” አለው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም “ተነስና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ” አለው፡፡ ወዲያውኑ ያሰው
 ድኖ አልጋውን ተሸክሞ ሄደ፡፡ ልጆች ታሪኩን በደንብ አነበባችሁ?
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጻጉዕን ከበሽታው እንደፈወሰው አነበባችሁ አይደል?
 ጎበዞች! እኛም በታመምን ጊዜ እንደመጻዕጉም የሚረዳን ሰው ባጣን ጊዜ እግዚአብሔር አምላካችን ይረዳናል፡፡
ደህና ሰንብቱ!

No comments:

Post a Comment